የዶክተር አብይ መንግስት ማድረግ ያለበት

Natenael Mekonnen

June 2021

ከሀገር አቀፍ የሰላም ሃይላት የቀረበ ግልጽ ደብዳቤ የተመረጠው የዶክተር አብይ መንግስት ማድረግ ያለበት:: 
 
#Ethiopia : አሁን ሁሉኑም ደምሳሽ ሃይላት በአሳማኝ ሁኔታ ሰጥ ለጥ እያደረገ በራሱ መቆሙን እያረጋገጠ የመጣው የጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ መንግስት የሂደት ለውጡን በልኩ በመመርመር ሊያደርግ ስለሚገባቸው ጉዳዮች ህዝብ በተለያየ መንገድ ሃሳቡን እያዋጣ ይገኛል።

የመጀመሪያው እና ቀዳሚው ጉዳይ ሊሆን የሚገባው የሰላም ማስፈኚያ መንገዶችን ለህዝባችን በተለያዩ ውሳኔዎች ማረጋገጥ ሊሆን ይገባል። የሰላም ማጣት ዋና ምንጭ የሆነው እና የህዝባችንን የዘመናት ተስፋ በጫንቃው ተሸክሞ እየተመነደገ ያለውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፍፃሜ በፍጥነት ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ይህንን ለማድረግ አደናቃፊ ሊሆኑ የሚችሉትን የሱዳን እና ተያያዥ የግብፅ ድንፋታን ለአንዴና እና መጨረሻ ጊዜ ማስቆም ያስፈልጋል። ይህንን ከባድ ውሳኔ ለመወሰን አዲስ ተመራጩ መንግስት ውስጣዊ ሰላምን ማምጣት ቀዳሚ ተግባሩ ሊሆን ይገባል። 

የትግራይ ጦርነት እና ተያያዥ ጉዳዮቹ በፍጥነት ማብቃት አለባቸው ። በቋፍ ላይ ካሉት የትግራይ ህዝብ ነጻአውጭ ግንባር/ትህነግ ቀሪ ሰላም ፈላጊ አካላት ጋር ድርድር በማድረግ ጦርነቱ በጊዜ ድምዳሜ ላይ እንዲደርስ መንግስታችን ቆራጥና ተከታታይ የደህንነት ፣ መከላከያና ሰላማዊ እርምጃዎችን መውሰድ ይጠበቅበታል። የህዳሴ ግድብ ፍፃሜን ለማረጋገጥ ውስጣዊ ሰላም መፍጠር የግድ ያስፈልጋል። ሱዳን እና ግብፅ ወደ ግልፅ ጥምረት በመሄድ አካባቢያዊ ነውጦችን ለማቀጣጠል ቆርጠው መነሳታቸው ከአለም አቀፍ ወዳጆች ተረጋግጧል። ሱዳን በተለይ የምትባለውን እና የሚነገራትን ትብብር ላይ የተመሰረተ እድገት ለመቀበል ፍቃደኛ አይደለችም ። የትህነግ አንዳንድ የነውጥ ሃይላትን በማስተባበር ከፍተኛ የጥቃት ዛቻ እና ልዩ ልምምድ ማድረግ መጀመሯም ታውቋል። ከትህነግ አካላት ጋር ሰላም መፍጠር እና የሀገር ውስጥ ደህንነትን በየድርድሩ በማረጋገጥ ከትግራይ ጀምሮ በቤኒሻንጉል ፣አማራ ፣አፋር ፣ ሶማሌ እና ኦሮሚያ ክልል ከሚንቀሳቀሱ ጽንፈኞች ጋር ድርድር በማድረግ ፖለቲካዊ መፍትሄዎችን በማቅረብ ውስጣዊ ሰላምን ለህዝባችን ማረጋገጥ ይገባል። 
ለባለብሩህ አእምሮው ጠቅላይሚኒስቴራችን ዶክተር አብይ ለመምከር ባንበቃም ያሉት ሀገርወዳድ አካላት አሁን ሁላችንም ይህንን ምርጫ አጠናቀናል መንግስት የሆነው ብልጽግናን በተለያዩ መንገዶች በማገዝ ስራ ሁሉም ሰላም ወዳድ ዜጋ ሊሰማራ ይገባል። ሱዳን እና ግብፅ ግልጽ ሀገራዊ ወቅታዊ ጠላቶቻችን ናቸው ። ሀገር ውስጥ ያለው የትኛውም ሃይል ሰላምን ማስቀደም እና ማረጋገጥ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባሩ ሊሆን ይገባል። 
ሰላም ለትግራይ ሰላም ለኢትዮጵያ፤  የሀገራችንን ሰላም ከተተበተበበት የጥላቻና እልህ ሳጥን አውጥተን በሀገር ዘላለማዊ ፍቅር በማሰዋብ ችግሮችን በድርድር መፍታት እና ሰላምን ማረጋገጥ ባህል እናድርገው!  ይቻላል!


 

የኢትዮጵያ ጉዶች

June 26, 2021

የኢትዮጵያ  ጉዶች::

አንቺ  ኢትዮጵያ የማትወልችው ጉድ የለም።   እንደ አጋጣሚ ዩቱብ ስከፍት ቴሌቪዥኔ ላይ የሚታየው ኢትዮ 360 የሚል ነው።   አቶ ኤርሚያስ  ለገሰ ዋቅጅራ ላንቃው እስከሚሰነጠቅ ሲጮህ አየሁና ቁጭ ብዬ ማየቱንና ማዳመጡን ጀመርኩ። የሚያወራው ባልደራስ ያሚባል ፓርቲ ለምን አዲስ አበባ ውስጥ እንደተሸነፈ ነው፤ ብዙ ምክንያቶችን ቢያትትም ሁለቱ 1) በመጀሪያ ምርጫው ተበልቷል ብሎ ስለአመነ 2)እስክንድር ስለአልተመዘገበ  እያለ ብዙ ምክንያቶችም ጨምሮ ይዘረዝራል:: 

ይቀጥልና  በአመሪካን አገር የምርጫ ሂደት ለፕሬዚዳንት፣ ለሴኔትና ለኮንግረስ እንዴት እንደሚካሄድ ሲያስረዳ ብዙ ጊዜ ያባክናል። ይኼ ሁሉ አላስፈላጊ ነው ::  ዓላማው ይመስለኛል ምን ያህል አዋቂ እንደሆነ ለማሳየት፣  ከጀርባው ብዙ የተደረደሩ መጻሕፍት ይታያሉ።  የኢትዮጵያ ምርጫ ፓርላሜንተሪያን ነው… ማለትም  ተመራጮች ፓርቲዎችን ይወክላሉ። እንግዲህ ከዚህ በፊት  እንደሰሰማሁት ከሆነ ኤርሚያስ  ለገሠ ዋቅጅራ በአሜሪካ አገር የባልደራስ ወኪል እንደሆነ ነው  የማውቀው። 

ይኼ የሚወስደኝ ኤርሚያስ ለገሠ ዋቅጅራ በ360 ሚዲያ ላይ እንደገልልተኛ ተንታኝ ሆኖ መቅረቡ… እራሱ ዳኛ …እራሱ ፈራጅ ኢትዮጵያውያኖች አንደሚሉት መሆኑ ነው::

በመጨረሻም የተገነዘብኩት ይኼ ሰውዬ ኢትዮጵያውያ ውስጥ ብጥብጥ እንዲነሳ የሚፈልግ ይመስላል።   ይኸንን ያለኩበት ምክንያት  ባልደራስና ሌሎቹ ፓርቲዎች የምርጫ ቦርድን እንዳይቀበሉ ይገፋፋል። የሰማሁት ይኼ ሰው ቁጥር አንድ የሕወሓት ካድሬ አንደነበር ነው።   የየሚታመን ነው  ወይ?  እንግዲህ  ኢትዮጵያውያ የማትወልደው ጉድ የለም የምለው ለዚህ ነው።  

እግዚአብሔር ኢትዮጵያውያን  ከማይታመኑ መልክተኞች ይጠብቃት። 

 

ወይዘሮ ፀዳለ ለማ

  ምንድን ናቸው?   የፖለቲካ አክቲቪስት ናቸው ወይስ ጋዜጠኛ /ጁርናሊስት ናቸው?

ዴሞክራሲ ቱዴይ (Democracy Today) የሚባል ትቪ ላይ ቀርበው በዚህ ሳምንት በትግራይ የኢትዮጵያ አየር ሃይል ባካሄደው የአየር ጥቃት በጣም እርግጠኛ ሆነው ጥቃቱ የተካሄደው  ሲቪሊያንን ኢላማ አድርጎ ነው ይላሉ:: ለዚህም መረጃቸው ገበያው ላይ የሚታዩ  ሰዎች የወታደር  ልብስ  አለመልበሳቸው ነው ይላሉ። 

እዚህ መደምደሚያ ላይ እንዴት ደረሱ?  የሕወሓት ተዋጊዎች ሸሽተው ጫካና ሕዝብ መሀል ከተበተኑ በኃላ የሚቀሰቅሱት የሲቪል ልብስ ለብሰውም ነው። 

ገበያው ላይ የሚታዩት በርግጥ ሲቪሏውያን ናቸው ወይ?  ወይዘሮ ፀዳለ ግን እርግጠኛ ሆነው ነው የሚናገሩት።   

ሌላ የሚገርመው ደግሞ ወይዜሮ ፀዳለ በዘገቯቸው ሁለት መከላከያ ሃይል ፤ሁለት መንግሥት እያሉ ሲያወሩ  ይኼ ዕውቀት በተጨባጭ ሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ አይደለም።   ከጋዜጠኝነት ይልቅ ወገንተኛ መሆናቸውን በግልጥ ስለጦርነቱ አጀማመር በማድበስበስ የተናገሩት ሕወሀት ነፃ ሲያደርጉ  ይታያሉ። 

ካለፈው ዝግጅታን ቅዳሜ የካቲት 9 2011

From Los Angeles hager wodad archive (Feb 16,2019)

አገሬን ከሩቅ ሳያት

የኢትዮጵያ 6ኛው አገራዊ ምርጫ በሰኔ 14 ሰኞ ሊካሄድ ሕዝቡ እሁድ እኩለ ሌሊት ላይ በመሰለፍ የምርጫ ሰዓት መድረስን ሲጠባበቅ  ማየቱ፣  ቀኑን ሙሉ ረጅም ሰልፍ ላይ ቆሞ በፀሐይና በዝናብ ደከመኝ ሳይል በትእግስት ተራውን ጠብቆ አንዳንዱ ደግሞ እስከ እኩለ ሌሊት ቆይቶ በመምረጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጨዋነቱን፣ ትዕግስቱንና ለዴሞክራሲ ያለውን ጥማት በተግባር አሳይቷል። ዐይን ላለው ለሚያይ፣ ጆሮ ላለው ለሚሰማ የምርጫው ሂደት በጣም የሚያስደስትና የሚያኮራ ነው። 

 ይኼ የሰኞ ሰኔ 14 ቀን የምርጫ ሂደት በጣም ብዙ ነገሮች የታዩበት ምርጫ ነው። በመጀመሪያ የምርጫ ቦርዱ ከመንግሥት ገለልተኛ መሆኑ የታየበት፤  ምርጫውን ማስተባበሩ በአገር ደረጃ ምን ያህል ከባድና ፈታኝ እንደሆነ ያሳየበት፤ አገሪቱ ባለችበት የፀጥታ ሁኔታ ይኸንን ምርጫ ማከናወኑ፤የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የዳበረና ባለሙያ (professional) ተቋም መሆኑ የታየበት ጊዜ ነው። ምርጫ ቦርዱ እንደተቋም ከነጉድለቱ ጥሩ ሥራ በመሰራቱ መመስገን ይገባዋል፡ ሰህተቶችይታረማሉ። 

እዚህ ላይ አንድ ነገር መጥቀሱ ተገቢ ነው፤  ከምርጫው በፊት ከዋሽንግተን አመሪካ እስከ አዲስ አበባ ድረስ የተለያዩ ሚዲያ ነን ባዮች ምርጫ ቦርዱን በመጥፎ ገፅታ ለማሳየትና ተቀባይነት እንዳይኖረው ያልፈነቀሉት ድንጋይ፣ ያልዋሹት ውሸት የለም። ምርጫ ቦርድ  በምርጫ ቀን አዋረዳቸው።   በምርጫው ቀን በቀጥታ የተለያዩ የኢትዮጵያ ሚዲያዎች የሚስተላልፉትን  ሥርጭት በምስልም ሆነ  በቃል የሚታይና  የሚሰማ ተዘናግተን እናሞኛችሁ በማለት ኢትዮጵያውያ ውስጥ የሚነውን እያቀረቡ ከሚታየውና ከሚስማው ተቃራኒ ኢትዮጵያውያንና ምርጫ ቦርድን ለማሳነስ ጥረት ሲያደርጉ ይታያሉ።   ፈረንጆች  ይኼንን ድርጊት pathetic  ይሉታል። 

◦ በሴ 14 ቀን ሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጨዋነትና ትዕግስተኛነት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሚዲያ ነፃ መሆኑን በአደባባይ በደንብ ያስመሰከረበት ቀነ። 

◦ የተለያዩ ጋዜጠኞች ትልቁን ትንሹን መራጭ ሲጠይቁ፣ ግለሰቦች መልስ ሲሰጡ ማየት በጣም ደስ ይላል፣ የመንግሥትና የግል ሚዲያ እኩል ሲሳተፉ ማየቱ ደግሞ የበለጠ ያረካል።

◦ ሌላኛው በሰኔ 14 የታየው የፖለቲካ ፓርቲዎች ጨዋነት (maturity) ነው።   ሁሉም ፓርቲዎች ያሳዩት ሃላፊነት በጣም የሚደነቅ ነበር።   ምርጫው በሰላም እዲጠናቀቅ ክፍተኛ አስተዋፆ አድርገዋል። 

◦ የኢትዮጵያ መንግሥትም ፀጥታን በማስከበር ምርጫው በሰላም እዲከናወን ሀላፍነቱን ተወጥቷል 

◦ ኢትዮጵያውያ ላይ የተጋረጠው የውጭ አገራት፣  የዓለም አቀፍ ድርጅቶችና እገር ውስጥ ካሉ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ማለትም ምርጫው እንዳይካሄድ ከሚፈልጉት ጋረ በመናበብና በመተባበር የሰኔ 14 ቀን ምርጫ እዲከሽፍከፍተኛ ዘመጃ መካሄዱ የማይረሳ ነው።  ሆኖም ኢትዮጵያውያ አሸንፋለች።  ምርጫውን አጠናቀናል፣ የግድባችንም ውሀ ሙለት ይካሄዳል፣ ሱዳንም ከመሬታችን ለቃ ትወጣለች። 

ኢትዮጵያውያ በልጆቿዋ ሃይል  ትከበራለች!! 

ሀገር ወዳድ::

Ethiopians Go to the Polls Even After the US Tells Them Not to

By Ann Garrison

On Monday, June 21st, Ethiopians went to the polls to select a parliament, which will elect a prime minister, even though US officials told them not to, warning of chaos and violence. Maybe they think it’s arrogant of the United States to presume to be the global arbiter of peace, justice, and democracy.

The African Union sent an election observer mission headed by former Nigerian President Olusegun Obasanjo, who told press  midday on Monday that it was going well, far better than previous Ethiopian elections.

Birtukan Mideksa, chair of the Ethiopian National Election Board

Lawyer, judge, and politician Birtukan Mideksa, chair of the National Election Board, no doubt agrees. In 2005, she helped found the Coalition for Unity and Democracy (CUD) Party, ran for parliament a second time, claimed the election was rigged, and was then among thousands imprisoned by the US puppet government of Prime Minister Meles Zenawi in the ensuing crackdown. She was sentenced to life in prison, pardoned in 2007—after signing a controversial document regretting past mistakes—but sent back to prison for life in 2008. International human rights advocacy, including that of Amnesty International, led to her release and exile in the United States, where she attended the Harvard Kennedy School of Government and spent time employed by the National Endowment for Democracy, the CIA cutout that claims to promote democracy around the world while in fact promoting US global hegemony.

It’s not clear whether her brief tenure with NED should be a red flag or simply something to keep in mind as her political career advances. The United States foreign policy establishment often likes to invest in any promising African leaders even if they are opposed to a government the US is supporting at the time, as was the case with Mideksa. And the leaders they invest in don’t always toe the line over time. Somali President Mohamed Abdullahi Mohamed, aka Farmaajo, is a case in point. Abiy, Farmaajo, and Eritrea’s President Isaias Afwerki are now alarming US political and military elites by forming an alliance and threatening to chart an independent path in the Horn of Africa.

In any case, Mideksa seems to be enjoying rock star status in Ethiopia today. The BBC ran a lengthy profile  of her including many of the aforementioned details.

Election could establish legitimacy of Prime Minister Abiy and the Prosperity Party

Sitting Prime Minister Abiy Ahmed’s Prosperity Party is widely expected to win a majority large enough to make him prime minister and increase both his legitimacy and the party’s. Abiy has served as Ethiopia’s caretaker prime minister since April 2018, when a popular uprising finally forced the Tigray People’s Liberation Front from power after 27 years. In 2019, he was awarded the Nobel Peace Prize for negotiating peace with Eritrea, a former Ethiopian colony.

Under the rule of the Tigray People’s Liberation Front, commonly known as the TPLF. EThiopia was a key US ally and military proxy in the Horn of Africa and on the African continent, putting boots on the ground under US command in both Somalia and South Sudan. The US and NATO have been hostile to Prime Minister Abiy, seemingly because of his alliance with Eritrea, the only African nation that refuses to cooperate with AFRICOM, the US Africa Command, or submit to the debt peonage that the International Monetary Fund and World Bank have imposed on other African nations.

Last year Prime Minister Abiy postponed elections because of the COVID-19 pandemic, but the US’s former ally, the TPLF, held elections in Tigray Regional State nevertheless and then attacked a federal army base in the state capital, Mekelle, ambushing and killing Ethiopian National Defense Forces who had been sleeping. Prime Minister Abiy responded, as any head of state would, by sending in the national army to put down the insurrection, and fighting is ongoing. Eritrea was drawn in after the TPLF fired rockets across its border at the Eritrean military.

Elections were not held on Monday in Tigray because of the civil conflict. They were reportedly not held in Somali State because of logistical problems or in Harrar City because of an unresolved lawsuit over who can vote. It was also reported that some did not vote in Benishangul-Gumuz region because ethnic violence prevented voter registration. However, these regions are all expected to elect parliamentary representatives by September, and many Ethiopians expressed enthusiasm for what they consider the country’s first real, competitive election. Fitsum Alemu, a member of the Ethiopian diaspora living in Virginia, told me that he didn’t expect the election to solve all of Ethiopia’s problems, but that voting was so important to members of his family that they stood in line for several hours in the rain to vote in Addis Ababa.

Benyam Kitaw, a member of the diaspora living in Los Angeles, said, “All the people I spoke with in Ethiopia stated that they are excited about voting and the prospect of true democracy starting to take hold there for the first time. Democracy may be bumpy and have flaws, but progress towards the common Ethiopian finally having their vote counted means that Ethiopia is closer to self-determination, and this is a very good thing.” 

US says an honest and peaceful election is impossible under current conditions, but Obama and Rice praised TPLF’s 100% “election victory”

Secretary of State Antony Blinken and USAID Chief and former UN Ambassador Samantha Power said that the Tigray conflict, and more, made an honest and peaceful election impossible and demanded that Abiy postpone the election.

However, in 2015, when Prime Minister Hailemariam Desalegn and the TPLF claimed to have won an impossible 100% of the vote, Barack Obama called it democratic. Susan Rice, who was then Obama’s National Security Advisor, addressed  reporters prior to their trip to Kenya and Ethiopia and said that the TPLF’s 100% victory suggested some procedural problems, but she didn’t doubt the rightness of the outcome. When a reporter asked whether she considered that an honest election, she responded “100%,” and then laughed, helping to make herself one of the most despised US officials in Ethiopia and on the African continent.

Ann Garrison is an independent journalist based in the San Francisco Bay Area. In 2014, she received the Victoire Ingabire Umuhoza Democracy and Peace Prize for promoting peace through her reporting on conflict in the African Great Lakes Region. Please help support her work on Patreon. She can be reached on Twitter @AnnGarrison and at ann(at)anngarrison(dot)com.

From the archives of Los Angeles Hager Wodad

እንኳን ደሰ አለሽ አገሬ 

የኢትዮጵያ 6ኛው አገራዊ ምርጫ በሰኔ 14 ሰኞ ሊካሄድ ሕዝቡ እሁድ እኩለ ሌሊት ላይ በመሰለፍ የምርጫ ሰዓት መድረሰን ሲጠባበቅ  ማየቱ፣  ቀኑን ሙሉ በረጅም ሰልፍ በፀሐይ በዝናብ ደከመኝ ሳይል በትእግስት ተራውን ጠብቆ አንዳንዱ እስከ እኩለ ሌሊት ቆይቶ በመምረጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጨዋነቱን፣ ትዕግስቱንና ለዴሞክራሲ ያለውን ጥማት በተግባር አሳይቷል። ዐይን ላለው ለሚያይ፣ ጆሮ ላለው ለሚሰማ የምርጫው ሂደት በጣም የሚያስደስትና የሚያኮራ ነው። 

 ይኼ የሰኞ ሰኔ 14 ቀን የምርጫ ሂደድ በጣም ብዙ ነገሮች የታዩበት ምርጫ ነው። በመጀመሪያ ምርጫ ቦርድ ከመንግሥት ገለልተኝነት የታየበት፤  ምርጫውን ማስተባበሩ በአገር ደረጃ ምን ያህል ከባድናፈታኝ እንደሆነ፤ አገሪቱ ባለችበት የፀጥታ ሁኔታ ይኸንን ምርጫ ማከናወኑ፤ የኢትዮጵያምርጫ ቦርድ የዳበረና ባለሙያ (professional) እንደተቋም የታየበት ጊዜ ነው። ምርጫ ቦርዱ እንደተቋም ከነጉድለቱ ጥሩ ሥራ በመሰራቱ መመስገን ይገቧል ሰህተቶችይታረማሉ።      

እዚህ ላይ አንድ ነገር መጥቀሱ ተገቢ ነው፤  ከምርጫው በፊት ከዋሽንግተን አመሪካ እስከ አዲስ አበባ ድረስ የተለያዩ ሚዲያ ነን ባዮች ምርጫ ቦርዱን ለማቀርሸትና ተቀባይነት እንዳይኖረው ያልፈነቀሉት ድንጋይ፣ ያልዋሹት ውሸት የለም። ምርጫ ቦርድ  በምርጫ ቀን አወረዳቸው።   በምርጫው ቀን በቀጥታ የተለያዩ የኢትዮጵያ ሚዲያዎች የሚስተላልፉትን  ሥርጭት በምስልምሆነ  በቃል የሚታይና  የሚሰማ ትተው እናሞኛችሁ በማለት ኢትዮጵያውያ ውስጥ የሚዶጓሟቸውን እያቀረቡ ከሚታየውና ከሚስማው ተቃራኒ ኢትዮጵያውያንና ምርጫ ቦርድን ለማቀርሸት ጥረት ሲያደርጉ ይታያሉ።   ፈረንጆች  ይኼንን ድርግት ፓተትክ ይሉታል። 

◦ በሴ 14 ቀን ሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጨዋነትና ትዕግስተኛነት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሚዲያ ነፃ መሆኑን በአደባባይ በደንብ ያስመሰከረበት ቀነ። 

◦ የተለያዩ ጋዜጠኞች ትልቁን ትንሹን መራጭ ሲጠይቁ፣ ግለሰቦች መልስ ሲሰጡ ማየት በጣም ደስ ይላል፣ የመንግሥትና የግል ሚዲያ እኩል ሲሳተፉ ማየቱ ደግሞ የበለጠ ያረካል።

◦ ሌላኛው በሰኔ 14 የታየው የፖለቲካ ፓርቲዎች ጨዋነት (maturity) ነው።   ሁሉም ፓርቲዎች ያሳዩት ሃላፊነት በጣም የሚደነቅ ነበር።   ምርጫው በሰላም እዲጠናቀቅ ክፍተኛ አስተዋፆ አድርገዋል። 

የኢትዮጵያ መንግሥትም ፀጥታን በማስከበር ምርጫው በሰላም እዲከናወን ሀላፍነቱን ተወጥቷል 

◦ ኢትዮጵያውያ ላይ የተጋረጠው የውጭ አገራት፣  የዓለም አቀፍ ድርጅቶችና እገር ውስጥ ካሉ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ማለትም ምርጫው እንዳይካሄድ ከሚፈልጉት ጋረ በመናበብና በመተባበር የሰኔ 14 ቀን ምርጫ እዲከሽፍከፍተኛ ዘመጃ መካሄዱ የማይረሳ ነው።  ሆኖም ኢትዮጵያውያ አሸንፋለች።  ምርጫውን አጠናቀናል፣ የግድባችንም ውሀ ሙለት ይካሄዳል፣ ሱዳንም ከመሬታችን ለቃ ትወጣለች። 

ኢትዮጵያውያ በልጆቿዋ ሃይል  ትከበራለች!! 

ሀገር ወዳድ::